Mamo E. Mihretu is the 10th Governor of the National Bank of Ethiopia (NBE). Before he was appointed as the Governor of NBE, Mr. Mamo served as the founding CEO of the Ethiopian Investment Holdings (EIH), the strategic investment arm of the government of Ethiopia.
የተረጋጋ ዋጋና የውጭ ምንዛሬ እንዲሁም ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት የማክሮኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት በመሆናቸው የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ እነርሱ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አዲሱ የባንኩ ገዥ አቶ ማሞ እስመለዓለም ምህረቱ ገለጹ፡፡ ከፋይናንስ ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ጋርም በዘርፍ የ 6 ወር አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት 127ኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት አከበሩ። የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በባንኩ አዳራሽ በተከናወነው ሥነሥርዓት ላይ የማኔጅመንት አባላትና የባንኩ ሠራተኞች፣ የተገኙ ሲሆን፣ በልዩ ልዩ ሁነቶች መርሐግብሩ ተከናውኗል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሴት ሠራተኞች የዘንድሮውን የዓለም የሴቶች ቀን በድምቀት አከበሩ። ቀኑ “እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ቃል በአገርአቀፍ ደረጃ ለ47ኛ ጊዜ ተከብሮ ውሏል።